
ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ከሚያስተደድራቸው ተቋማት የተወጣጡ ሰራተኞች የኢትዮጵያ የክፍያ መንገዶች ኢንተርፕራይዝ የተሰሩ እና እየተሰሩ ያሉ ፕሮጀክቶችን ጎበኙ።
================================
ኢክመኢ[ETRE ጥር 15/2018 ዓ/ም]
ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ በስሩ ካሉ ተቋማት የተውጣጡ ሰራተኞች በቀን 14/05/2018 ዓ/ም በኢትዮጵያ የክፍያ መንገዶች ኢንተርፕራይዝ ተገኝተው በኪሎ ሜትር 29 ላይ የተሰራው የአገልግሎት መስጫ ጣቢያ እና አሁን ተግባራዊ ለማድረግ በዝግጅት ላይ ያለውን የቴክኖሎጂ የኢንተለጀንት ትራንስፖርት ሲስተም (ITS) ጉብኝት አደረጉ ፡፡
በጉብኝቱ ኢንተርፕራይዙ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እና በዲጅታላይዜሽን መስክ እያካሄደው ያለውን ለውጥ እንዲሁም ለተገልጋዮቹ ምቾት እየሰጠ ያለውን ትኩረት ለተሳታፊዎች አሳይቷል።


